የኢትዮጵያዊያኑ የሰሜን አሜሪካ ስፖርት ግጥሚያዎች ተጀመሩ

Your browser doesn’t support HTML5

የቴክሳሷ ዳላስ ከተማ ላይ የተዘጋጀው የዘንድሮው 35ኛው የሰሜን አሜሪካ የኢትዮጵያዊያን ስፖርትና ባሕል ፌዴሬሽን መክፈቻ ሥነ-ሥርዓት በአዲስ አበባ ሰዓት ከሌሊቱ ሰባት ሰዓት ላይ ይጀመራል። የፌደሬሽኑ የዘንድሮ የክብር እንግዶች የቀድሞ ቦክሰኛው ሻምበል አየለ መሃመድ፤ ጋዜጠኛው እስክንድር ነጋና የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድንን ለመካከለኛውና ምሥራቅ አፍሪካ ዋንጫ ያበቁት የቀድሞ አሠልጣኝ አቶ አባይነህ ደስታ መሆናቸው ታውቋል።