“ጠቅላይ ሚኒትሩን ለመደገፍ የወጡ ልጆቼን ፍለጋ ወጥቼ በጥይት ተመታሁ”

Your browser doesn’t support HTML5

በቤንሻንጉል ጉምዝ ማኦ ኮሞ ወረዳ ቶንጎ ከተማ ለጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አሕመድ የድጋፍ ሰልፍ የወጡ ነዋሪዎች በክልሉ ልዩ ፖሊስ ታጣቂዎች በተተኮሰ ጥይት የሁለት ሰው ሕይወት ማለፉንና 40 ሰዎች መቁሰላቸውን ነዋሪዎችና የአጎራባች ወራዳ ፖሊስ ኃላፊዎች ገለጹ።