ከሃያ ዓመታት በኋላ የኤርትራ ልዑካን አዲስ አበባ ገቡ

  • እስክንድር ፍሬው

Your browser doesn’t support HTML5

የኤርትራ መንግሥት ከፍተኛ የልዑካን ቡድን ከሃያ ዓመታት በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ አዲስ አበባ ገብተዋል፡፡ በጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አሕመድ የቀረበውን ጥሪ ተከትሎ ሁኔታዎችን ለመርመር የመጣው የልዑካን ቡድን የኤርትራ ፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ ከፍተኛ አማካሪ የማነ ግብረአብና የሀገሪቱ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ኦስማን ሳላህ የሚገኙበት ነው፡፡