ሞያሌ አካባቢ ትምህርት እየተስተጓጎለ ነው

Your browser doesn’t support HTML5

ኢትዮጵያ ውስጥ የአሥረኛና የአሥራ ሁለተኛ ክፍሎች ተማሪዎች ፈተና በሚወስዱበት ጊዜ በኦሮምያና በሶማሌ ክልሎች አዋሣኝ አካባቢዎች ውስጥ “የሶማሌ ክልል ልዩ ኃይል ያደርሰዋል” በሚባል ጥቃት ምክንያት ብዙ ትምህርት ቤቶች መዘጋታቸውንና የብዙ ሺህ ተማሪዎች የትምህርት ሂደት መስተጓጎሉን የአካባቢው ነዋሪዎችና ባለሥልጣናት ለአሜሪካ ድምፅ ተናግረዋል።