“ጋዜጠኞችን መፍታት ብቻውን የፕሬስ ነፃነትን አያረጋግጥም” - ጋዜጠኞችና ሲፒጄ

Your browser doesn’t support HTML5

ኢትዮጵያ ጋዜጠኞችን ዝም ለማሰኘት የምትጠቀምበትን አፋኝ ሕጎቿን ካላሻሻለች፣ የመጻፍና የመናገር ነፃነትን የምታፍንበትን የእጅ አዙር አስጨናቂ አካሄድ ካላስተካከለች፣ጋዜጠኞችን ከእስር መልቀቋ ብቻ ነፃ ሀገር ሊያሰኛት አይችልም ሲል ዋና ቢሮውን በዚህ በዩናይትድ ስቴትስ ያደረገው የጋዜጠኞች ደህንነት ተሟጋቹ በእንግሊዘኛው ምሕፃረ ቃል (CPJ) አስታወቀ።