በድጋሚ የታሰሩት ዐሥራ አንድ ሰዎች ጉዳይ
Your browser doesn’t support HTML5
በቅርብ ግዜ ከእስር የተፈቱትን እስክንድር ነጋን፣ አንዷለም አራጌንና ተመስገን ደሳለኝን ጨምሮ አያሌ ሰዎች አዲስ አበባ ጎተራ አካባቢ በሚገኝ ፖሊስ ጣቢያ በኮማንድ ፖስቱ ትዛዝ ታስረው እንደሚገኙ ታወቀ። ፖሊስ ተጠርጣሪዎቹ በኮማንድ ፖስቱ ትዛዝ ከመታሰራቸው የተለየ ሌላ መረጃ እንደሌለው ተናግሯል።