ታዋቂዎቹ እስረኞች የይቅርታ ፎርም እንደማይፈርሙ መግለፃቸውን ቤተሰቦቻቸው ተናገሩ

Your browser doesn’t support HTML5

ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ፣ አቶ አንዱዓለም አራጌንና አቶ ክንፈ ሚካኤል ደበበ (አበበ ቀስቶ) ከእስር ለመፈታት የግንቦት ሰባት አባል መሆናቸውን አምነው የይቅርታ ፎርም ላይ እንዲፈርሙ መጠየቃቸውን ለቤተሰቦቻቸው ገለፁ። በሌላ በኩል በይቅርታ እንዲፈቱ የተወሰነላቸው 417 ታራሚዎች ዝርዝር ለውሳኔ ወደ ሀገሪቱ ርዕሰ ብሄር መላኩን የፌደራል ጠቅላይ አቃቤ ሕግ ምንጮች ገልፀዋል፡፡