የጋዜጠኛ እክስንድርና የአቶ አንዷለም ቤተሰቦች በሰሙት ዜና መደሰታቸውን ገለፁ

Your browser doesn’t support HTML5

ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋና አቶ አንዱዓለም አራጌን ጨምሮ 746 እስረኞች በይቅርታና ክሳቸው ተቋርጦ እንዲለቀቁ መወሰኑ የሀገር ውስጥ መገናኛ ብዙሃን ዘግበዋል። የጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ ባለቤት ሰርካለም ፋሲል፤ ዜናውን ከሰማች በኋላ በጣም መደሰቷን ለአሜሪካ ድምፅ ተናግራለች። የአቶ አንዷለም አራጌ ባለቤት ዶ/ር ሰላም አስቻለው በበኩሏ ካየች ብኋላ እንደምታረጋግጥ ተናግራለች።