ዶናልድ ትረምፕ በኮንግረስ ቃናቸው ይዘልቁ ይሆን?

Your browser doesn’t support HTML5

የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትረምፕ ከትናንት በስተያ ለተወካዮች ምክር ቤቱ ጥምር ጉባዔ ያደረጉት ንግግር በተከታተሉት አሜሪካዊያን በአመዛኙ አዎንታዊ አቀባበል ማግኘቱ እየተሰማ ነው። ፕሬዚዳንቱ በንግግራቸው ላይ መተባበርና የሁለቱንም ገዥ ፓርቲዎች የጋራ ውሣኔዎች መጠየቃቸው ብዙ ሪፐብሊካንን አስደስቷል።ዴሞክራቶቹ ግን በትረምፕ እውነተኛ አቋም ላይ ጥርጣሬአቸው እንደበረታ ነው።