የበቀለ ገርባ ጉዳይ እንደገና ተቀጠረ

  • መለስካቸው አምሃ

Your browser doesn’t support HTML5

የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግሬስ /ኦፌኮ/ ተቀዳሚ ምክትል ሊቀመንበር አቶ በቀለ ገርባ ለዋስ መብታቸው መታገድ የሰጡት መልስ "ተገቢ ያልሆነና ሕግን ያልተከተለ ነው" ሲል ፌደራል ጠቅላይ ዓቃቤ ሕግ መልስ ሰጠ፡፡ የፌደራሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት በአቶ በቀለ ላይ የፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት የሰጠውን ውሣኔ እንዲያፀናም ጠይቋል፡፡