በኢትዮጵያ የድንገተኛ ቀዶ ሕክምና ሞያተኞች እሮሮ

Your browser doesn’t support HTML5

በእናቶች ሞት ቅነሳ ከፍተኛ አስተዋፆ ካበረከቱ በኋላ ሞያቸውንና ራሳቸውን ለማሳደግ የሚችሉበት ከፍተኛ ትምሕርት እንዳያገኙ መከልከላቸውን፣ ይህን ለማድረግ የሚያችል የትምሕርት ክፍል እንደሌለም በኢትዮጵያ የተቀናጀ ድንገተኛ ቀዶ ሕክምና ሞያተኞች ገለጹ። የጤና ጥበቃ ሚኒስትር መሥሪያቤት ሚኒስትሮች በተቀያየሩ ቁጥር የተገባላቸው ቃል እንደታጠፈም ተናግረዋል። “ታማኝ አገልጋይ ብቻ ተደርገን የተተውን ሰዎችን ነን”ሲሉም አማረዋል።