“በሼኩ የሚንቀሳቀሱ የውጭ ሀገር የንግድ ተቋማትን ሥራ አያስተጓጉልም” – የሼክ መሐመድ ቃል አቀባይ

Your browser doesn’t support HTML5

የሳውዲ አረቢያ መንግስሥት በሙስና ከጠረጠራቸውና በቁም እስር ከሚገኙት የመንግሥት ባለስልጣናትና ነጋዴዎች መካከል የሚገኙት ኢትዮጵያዊ ትውልድ ያላቸው የሳውዲ ቱጃር ሼክ ሞሐመድ ሁሴን አሊ አል-አሙዲ በሳውዲ መንግሥት እየተመረመሩ መሆኑንና የታገደው ንብረታቸው ከሳውዲ ውጪ ያለን አያካትትም ሲሉ ለንደን የሚገኙት የሼኩ ቃል አቀባይ ለአሜሪካ ድምፅ ገለፁ።