በዮናታን ላይ የተላለፈው ውሳኔ የመናገር ነፃነትን የሚፃረርና “አሳፋሪ” ነው ሲል አምነስቲ ገለፀ

  • ሔኖክ ሰማእግዜር

Your browser doesn’t support HTML5

በእስር ላይ የሚገኘው የቀድሞው የሰማያዊው ፓርቲ የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ዮናታን ተስፋዬ ላይ ሽብርተኝነትን በማበረታታት በሚል በቀረበበት ክስ የተላለፈው የጥፋተኝነት ውሳኔ ሐሳብን የመግለፅና እና በፌስቡክ ፁሑፎችን የማውጣት መብት የሚፃረር “አሳፋሪ” ውሳኔ ነው ሲል ዓለም አቀፉ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅት አምነስቲ ገለፀ።