"በቂሊጦ ቃጠሎ ወቅት ጠባቂዎች ወደ እስረኞች ተኩሰዋል" - ሰብዓዊ መብት ኮሚሽን

Your browser doesn’t support HTML5

በቂሊንጦ ማረሚያ ቤት በተነሰሳው የእሳት ቃጠሎ ወቅት የማረሚያ ቤቱ ጠባቂዎች በእስረኛው ላይ ከውጭ ወደ ውስጥ ተኩሰው እንደነበርና አስለቃሽ ጭስም ወርውረው እንደነበር የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽን ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሕግ፣ ፍትሕና አስተዳደር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አባላት ሪፖርት አቀረበ። በዚሁ መሰረት ድርጊቱን የፈፀሙት የማረሚያ ቤቱ ጠባቂዎችና ትዕዛዙን የሰጡት ኃላፊዎች በሕግ ሊጠየቁ ይገባል ብሏል።