“የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ባይታወጅ ኖሮ የት ነው የሚቆመው አመጹ? የት ነው ጋብ የሚለው ነገር በጣም አጠያያቂ ነው የነበረው።” አቶ አታክልት አምባዬ።
“የአስቸኳይ ጊዜውን አዋጁን ያወጁትም ሰዎች መፍትሔው እንፈልጋለን መፍትሔ አልተፈለገም። መፍትሔው ምንድ ነው? ችግሩ ምንድነው? የሚለው ነገር ላይ ውይይት አላየንም።” አቶ ፈቃደ ሸዋ ቀና።
ዋሺንግተን ዲሲ —
Your browser doesn’t support HTML5
Your browser doesn’t support HTML5
በወቅታዊ የኢትዮጵያ ፖለቲካ ጉዳዮች ላይ ያተኮረው ክርክር በአስቸኳይ ጊዜው አዋጅ ወቅት በመንግስት የተወሰዱ እርምጃዎች አንድምታ እና ድሕረ-አስቸኳይ ጊዜ የተለያዩ ቀጣይ ሁኔታዎች ይዳስሳል።
የክርክሩ ተሳታፊዎች፤ አቶ አታክልት አምባዬ፤ የፍኖተ-ሰሜን የአማርኛና የትግርኛ ወርሃዊ መጽሄት አሳታሚና የፍኖተ ትንሳኤ ሚዲያና አሳታሚ ድርጅት ባለቤት፤ ከአዲስ አበባ።
አቶ ፈቃደ ሸዋ ቀና በዩናይትድ ስቴትሱ ብሔራዊ የጤና ምርምር ተቋም በጥናት ሥራ የተሰማሩና በኢትዮጵያ የፖለቲካ ጉዳዮች በመጻፍ የሚታወቁ ናቸው።