ኢትዮጵያ ጋዜጠኞችን በማሰር ከአፍሪካ ሦስተኛ ሆናለች

  • ቆንጂት ታየ

Your browser doesn’t support HTML5

ዋና መቀመጫውን በዩናይትድ ስቴትስ ያደረገው የጋዜጠኞች ደህንነት ተሟጋቹ(CPJ) ዓመታዊ በእስር ላይ ያሉ ጋዜጠኞችን ቁጥር ቀምሮ ይፋ በሚያደርግበት ዓመታዊ ሪፖርቱ በዚህ ወር በሚጠናቀቀው የአውሮፓውያን 2016 ዓ.ም በዓለም ዙሪያ 259 ጋዜጠኞች ታስረው እንደሚገኙ አስታውቋል። በዚህ ሪፖርቱ ከአፍሪካ ግብጽ 25 ጋዜጠኞችን በማሰር 1ኛ፣ ኤርትራ 17 ጋዜጠኞችን በማሰር ሁለተኛና ኢትዮጵያ 16 ጋዜጠኞችን በማሰር ሦስተኛ ሀገር ተብላለች።