አቶ በቀለ ገርባን ጨምሮ በሽብር ወንጀል የተከሰሱ የኦፌኮ ፓርቲ ታሳሪዎች አምስቱ በቀጠሮ ቀን ሳይቀርቡ ቀረ
Your browser doesn’t support HTML5
አቃቢ ሕግ እነ አቶ በቀለ ገርባን ጨምሮ በሽብር ወንጀል ከከሰሣቸው ሃያ ሁለት የኦሮሞ ፌዴራሊስት ኮንግረስ አመራር አባላትና ደጋፊዎች መካከል አምስቱ ዛሬ ፍርድ ቤት ሳይቀርቡ ቀሩ፡፡
ተጠርጣሪዎቹ ወደ ፍርድ ቤት ተገደው የመጡና ከፍተኛ ድብደባ እንደተፈፀመባቸውም ተናገሩ፤ ፍርድ ቤቱ ተከሳሾቹ ተሟልተው እንዲቀርቡ ትዛዝ ሰጥቶ ተለዋጭ ቀጠሮ ቆርጧል፡፡