“ባህር እንዲህ ከፍሎንም እንባችንና ሳቃችን አንድ መኾኑ አስገርሞኛል” ገጣሚና ደራሲ በረከት በላይነህ

Your browser doesn’t support HTML5

በኢትዮጵያ በተለይ ወጣቶችን በማህበራዊና ፖለቲካዊ ጉዳዮች እንዲነቁ በማስቻሉና በውስጠ ወይራ መልእክቱ የሚታወቀው “ፌስታሌን” የተሰኘው አንድ ሰው ብቻውን የሚተውንበት የሙሉ ሰዓት የመድረክ ተውኔት ወደ ዩናይትድ ስቴይትስ መጥቷል። በትናንትናው ዕለትም ዋሽንግተን ዲስ ውስጥ 900 ሰው ተመልክቶታል።