የሰመጉ የገቢ ማሰባሰቢያ ፕሮግራም ተቋረጠ
Your browser doesn’t support HTML5
የሰብዓዊ መብቶች ጉባዔ ለዛሬ፤ ዕሁድ ጥቅምት 13/2009 ዓ.ም ያዘጋጀውና እያካሄደ የነበረው የገቢ ማሰባሰቢያ መርኃግብር ሳይጠናቀቅ በፀጥታ ኃይሎች ተቋርጧል፡፡ የጉባዔው መሪዎች “የመንግሥትን ስም እያጎደፋችሁ ነው” የሚል ተግሣፅ ተሰጥቷቸው መለቀቃቸውን የሥፍራው የነበረው የአዲስ አበባ ዘጋቢያችን መለስካቸው አምሃ ገልጿል፡፡