“ሟቹም ኤፍሬም እናቱም ወ/ሮ ታደሉ የከተማችን ነዋሪዎች ናቸው” የዞኑ የኮሙዩኒኬሽን ኃላፊ

Your browser doesn’t support HTML5

ልጃቸው አስከሬን ላይ እንደተደበደቡ ለአሜሪካ ድምፅ የተናገሩት እናት በተባለው ቤት እንደማይገኙ የመንግሥት ኮሙዩኔኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ መሐምድ ሰኢድ መናገራቸው ይታወሳል። የዞን ኮሙዩኔኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ኃላፊ ደግሞ ሟቹም ኤፍሬምም እናቱም ወ/ሮ ታደሉ የከተማው ነዋሪዎች መሆናቸውን ተናግረዋል። ኮሙዩኔኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት የሉም የተባለው በመረጃ ክፍተት መሆኑን በፌስቡክ ገጹ ላይ አስፍሯል።