“የቴክኖሎጂ ዘመን በመኾኑ መሳሳትና መዋሸት ጉዳቱ ለራስ ነው” የጋዜጠኝነት መምሕራን

Your browser doesn’t support HTML5

ሰሞኑን የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽና በመንግሥት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት የተሠራጩትን የተሳሳቱ ፎቶግራፎች በተመለከተ ባልደረባችን ጽዮን ግርማ “እንዲህ ያሉ ስሕተቶች ምን ያሳያሉ?” የሚል ጥያቄን አንስታ በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የጋዜጠኝነትና ኮሙዩኒኬሽን መምሕር አቶ አቤል አዳሙንና በዩናይትድ ስቴትስ ኦሪገን ዩኒቨርስቲ የጋዜጠኝነት ኮሙዩኒኬን የዶክትሬት ተማሪ አቶ እንዳልካቸው ኃይለ ሚካኤልን አነጋግራ ተከታዩን ዘገባ ሠርታልች።