"በቀላሉ ቢገደብ ኖሮ እርሻችንን በጎርፍ አናጣም ነበር" የመቂ ገበሬዎች
Your browser doesn’t support HTML5
ከአዲስ አበባ 131 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በሚገኘው መቂ አካባቢ ባሉ እርሻ ቦታዎች ቦታውን ስቶ የገባ ጎርፍ እርሻቸውን በሙሉ ከጥቅም ውጭ እንዳደረገባቸው የአካባቢው ገበሬዎች ይናገራሉ። እንዲህ ያለ የጎርፍ አደጋ ቀድም ብሎ ተከስቶ ያውቅ ስለነበረም ቦታው በአፈር እንዲገደብ አስቀድመው ጠይቀው ሰሚ አለማግኘታቸውን ይገልፃሉ። የአካባቢው አስተዳደድር በተፈጥሮ የመጣ ስለኾነ ምንም ማድረግ አይቻልም ይላል።