አስራ አንድ ህጻናት በሰሜን ምስራቅ ናይጄሪያ እስር ቤት እንደሞቱ አምነስቲ ኢንተርናሺናል ገለጸ

Your browser doesn’t support HTML5

ናይጄሪያ ውስጥ ተጠርጣሪ የጽንፈኛ እስላማዊው ቦኮ ሃራም አባላት በሚታሰሩበት ወታደራዊ የእስር ማዕከል በከበደ ጉስቁልና የነበሩ ቁጥራቸው ውደ አስራ ሁለት የሚጠጋ ልጆች፣ ህጻናትም ጭምር በዚህ የአውሮፓውያን ዓመት መሞታቸውን አምነስቲ ኢንተርናሺናል አስታወቀ። ለሰብአዊ መብቶች ከበሬታ ተሙጋቹ ድርጅት ናይጄሪያን በተደጋጋሚ ሲከሳት ቆይቷል። የናይጄሪያ መንግስት በበኩሉ ክሶቹን ያስተባብላል። ቦኮ ሃራምን በስኬት ድል እየመታሁ ነኝ ይላል።