በደቡብ ሱዳን በተቀሰቀሰ ውጊያና የምግብ ዕጥረት ብዙ ሺህ ህዝብ ወደ አጎራባች ሃገሮች እየተሰደደ ነው

Your browser doesn’t support HTML5

ደቡብ ሱዳን ውስጥ ካሁን ቀደም ሰላማዊ በነበሩ አካባቢዎች በተቀሰቀሰ ውጊያና ከባድ የምግብ ዕጥረት ምክንያት ብዙ ሺህ ህዝብ ወደ አጎራባች ሃገሮች መሰደዱን የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የስደተኞች ከፍተኛ ኮሚሽን አስታወቀ። እኛም ሆንን ሌሎች የሰብዓዊ ርዳታ ድርጅቶች ለስደተኞቹ ህይወት አድን አገልግሎት የምናውለው ገንዘብ እየተሟጠጠብን ነው ሲል ዩኤን ኤች ሲ አር (UNHCR) አስጠንቋል።