በሞያሌ በደረሰ የጎርፍ ማጥለቅለቅ ሶስት ሰዎች ሞቱ ንብረት ወደመ

Your browser doesn’t support HTML5

ባለፈዉ እሁድ በሞያሌ ከተማ የጣለ ከባድ ዝናብ በሰዉ ህይወትና በንብረት ላይ ጉዳት አደረሰ። ዝናቡን ተከትሎ በአካባቢዉ በደረሰ ከባድ ጎርፍ ማጥለቅለቅ የሶስት ሰዎች ሕይወት መጥፋቱን የአካባቢዉ የቀይ መስቀል ባልደረባ ለአሜርካ ድምጽ ተናግረዋል። ሜጋ በምትባል አነስተኛ መንደር አካባቢ ድልድይ እንዲሰራለት ተገድቦ የነበረ ወንዝ ከመጠን በላይ ሞልቶ በንብረት ላይ ጉዳት ማድረሱን ጠቅሶ፣ ገልሞ ዳዊት ተጨማሪ ከናይሮቢ አድርሶናል።