አል-ሸባብ በጋሪሳ ላይ የፈጸመው ጥቃት ቅዳሜ አመት ሊሆነው ነው
Your browser doesn’t support HTML5
ኬንያ በሚገኘው ጋሪሳ ዩኒቨርሲቲ ላይ የተፈጸምው የአሸብሪዎች ጥቃት በመጪው ቅዳሜ አንድ አመት ይሆነዋል። የዐል ሸባብ አማጽያን በዩኒቨርሲቲው በከፈቱት ጥቃት 148 ሰዎች ተገድለዋል። አብዛኞቹ ተማሪዎች ነበሩ። ኬንያ ለእንደዚህ አይነት ጥቃት ምላሽ የመስጠት ብቃትዋን እንዳጠናከረች ገልጻለች።