የኬንያ አትሌቶች በካርዲፍ ዩኒቨርሲቲ ዓለምአቀፍ ውድድር አሸነፉ

Your browser doesn’t support HTML5

በታላቋ ብሪታንያ ስመ-ጥሩ የካርዲፍ ዩኒቨርሲቲ ባስተናገደው የዓለም ግማሽ ማራቶን ሻምፒዮና ውድድር የኬንያ አትሌቶች የበላይነቱን ተቀዳጅተዋል። ​​በሴቶቹ ሦስቱንም ሜዳልያ ጠራርገው ወስደዋል። በእግር ኳሱ ስፖርት ለአፍሪካ ዋንጫ በመካሄድ ላይ ያለው ማጣሪያ ተጠናክሮ ቀጥሏል። የኢትዮጵያ የሴቶቹ ቡድን ማጣሪያውን አላለፈም። ዋሊያዎች ነገ በአዲስ አበባ ለአልጄሪያ አቻቸው ጋር በሚያደርጉት የመልስ ግጥሚያ ይለይላቸዋል ተብሏል።