“ኮሚቴ አቋቁመን ሁኔታውን እያጣራን ነው” አቶ ፍሰሃ ጋረደው የደቡብ ክልል ፖሊስ ኮሚሽነር

Your browser doesn’t support HTML5

ካለፈው እሁድ ጀምሮ በማኅበራዊ ሚድያ ሲሰራጩ የቆዩት፤በደቡብ ክልል በኦሞ ዞን የሚገኙ አራት ኢትዮጵያዊያን እርስ በርስ እግር ለእግርና አንገት ለአንገት በቃጫ ገመድ ታሥረውና እንግልት ደርሶባቸው የሚያሳዩ ፎቶግራፎችን በተመለከተ የክልሉ ፖሊስ ኮሚቴ አቋቁሞ እያጣራ እንደኾነ ሲገልፅ አንድ የሱርማ ነዋሪ ፤ ያስቸገረን ወንጀለኛን በገመድ አስሮ መያዝ በሱርማ የተለመደ እንደኾነ ይናገራሉ፡፡ ጽዮን ግርማ ተከታዩን ዘግባለች፡፡