የሶማልያንና የኤርትራን ጉዳይ የሚከታተለው ተቆጣጣሪ ቡድን ሶማልያን በምታሳየው ትብብር ሲያሞግስ ኤርትራን ግን ነቀፈ

Your browser doesn’t support HTML5

የተበበሩት መንግስታት ድርጅት የጸጥታ ምክር ቤት የወሩ ተረኛ ሊቀ-መንበርና ሶማልያንና ኤርትራን በሚመለከት የማዕቀብ ኮሚቴ ሊቀመንበር ራፋኤል ዳርዮ ራሚሪዝ ካሬኖ በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የተሰየመው ተቆጣጣሪ ቡድን ሶማልያንና ኤርትራን በሚመልከት ያቀረውን ዘገባ ባለፈው ሀሙስ ለጸጥታው ምክር ቤት አባላት አሰምተዋል። የኤርትራ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በበኩሉ ባወጣው መግለጫ ምላሽ ሰጥቷል።