ኢትዮጵያዊው ተመራማሪ የኮቺኔል ትል (የበለስ መዥገር) የሚያጠፋ መድሐኒት ቀመሙ

  • ግርማይ ገብሩ

Your browser doesn’t support HTML5

በ2003 ዓ.ም. ወደ ኢትዮጵያ በተለይ ደግሞ ወደ ትግራይ ክልል የገባው ትሉ ከፍተኛ ጥቅም ይገኝበታል በሚል ታቅዶ እንዲገባ መደረጉን በመቐለ ዩኒቨርሲቲ ተመራማሪና ተባባሪ ፕሮፌሰር ዶክተር ሲሳይ ወልደገብርኤል ይገልፃሉ። የኮቺኔል ትል የሚራባው በበለስ ተክል እንደመሆኑ መጠን በለስ ደግሞ ኢትዮጵያ ውስጥ ለሰውና እንስሳት ምግብነት ስለሚውል ትሉ ተክሉን በአጭር ዓመታት ውስጥ አውድሞታል።