የዑጋንዳ ዋናው የተቃዋሚ መሪ በሁለት ቀናት ውስጥ ለሁለተኛ ጊዜ ዛሬ በፖሊስ ቁጥጥር ሥር ዋሉ

Your browser doesn’t support HTML5

የዑጋንዳ ዋናው የተቃዋሚ መሪ ኪዛ ቤሲጄ በሁለት ቀናት ውስጥ ለሁለተኛ ጊዜ ዛሬ በፖሊስ ቁጥጥር ሥር ዋሉ። ቤሲጄ ዛሬ በተካሄደው ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ ላለፉት ሠላሣ ዓመታት ሥልጣን የኖሩትን ዮዌሪ ሙሴቬኒን በርቀት ተከትለው ሁለተኛ ደረጃ ላይ እንደሚገኙ ማምሻውን እየወጡ ያሉ የድምፅ ቆጠራ ውጤቶች እያመለከቱ ነው።