የኬንያ ፍርድ ቤት የኢትዮጵያ ስደተኞችን ወደ አገር መለሰ

Your browser doesn’t support HTML5

በሕገ ወጥ መንገድ የኬንያን ድምበር ተሻግራችሁዋል በመባል የተከሰሱ ከ28 በላይ የሚሆኑ ኢትዮጵያዉያን ኦሮሞ ስደተኞች ወደ አገራቸዉ እንዲመለሱ የማርሳቢት ፍርድ ቤት መወሰኑ ታዉቋል። ዓለም አቀፉ የስደተኞች ድርጅት (UNHCR) ስደተኞቹ ጥገኝነት እንዲያገኙ ለኬንያ መንግስት ያቀረበዉ ጥያቄ አንድ ስደተኛ ከማስጠልል በስተቀር ተቀባይነት እንዳላገኘ ተናግሯል። እንዲመሰሱ የተደረጉት ስደተኞች ግን አሁን ያሉበት ሁኔታ አልታወቀም።