በኦሮሚያ ከተሞች የሚካሄድ ተቃዉሞ ቀጥሏል

Your browser doesn’t support HTML5

የአዲስ አበባና የፊንፊኔ ዙሪያ የተቀናጀ ማስተር ፕላን ተግባራዊ ይደረጋል መባሉን ተከትሎ በኦሮሚያ ከተሞች ከሕዳር ወር አጋማሽ ጀምሮ ሲካሄድ የነበረዉ ተቃዉሞ ዛሬም በአንዳንድ አካባቢዎች ቀጥሏል። ተቃዋሚዎቹ፣ የታሰሩ እንዲፈቱ ለተገደሉት ሰዎች ቤተሰቦች ካሳ እንዲከፈል የሚል መፈክርም ጨምረዋል።