የኢትዮጵያ መንግሥት ያሰራቸዉን ሰላማዊ ተቃዋሚዎች በፍጥነት እንዲፈታ አምነስቲ ኢንተርናሽናል ጥሪ አቀረበ

Your browser doesn’t support HTML5

የኢትዮጵያ መንግስት ያሰራቸዉን ሰላማዊ ተቃዋሚዎች በአስቸኳይ እንዲፈታ ዓለም አቀፉ የመብት ተቆርቋሪ ድርጅት አምነስቲ ኢንተርናሽናል እስከ ፊታችን የካቲት 9, 2008 ዓለም አቀፍ ማህበረስብ ለኢትዮጵያ ባለስልጣናት ደብዳቤ እንዲጽፍ ጥሪ አቀረበ። ሰላማዊ ተቃዋሚዎችን መፍታት አለበት ሲል ጥሪ አድርጓል። የታሰሩት የተቃዋሚ ፓርቲ አመራር አባላት ተማሪዎች ጋዜጠኞችና ሌሎች በኢትዮጵያ እስር ቤት ዉስጥ ስቃይ እየተፈጸመባቸዉ ነዉ የሚል ስጋቱን አሰምቷል ድርጅቱ።