የምሥራቅ ኦርቶዶክ ክርስትና አማንያን የልደት በዐል

Your browser doesn’t support HTML5

የጌታችንና የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ የልደት መታሰቢያ በዐል ዋዜማ ዛሬ ታኅሣሥ 27 ቀን 2008 ዓም በመላው ዓለም በሚገኙ የምሥራቅ ኦርቶዶክስ ሃይማኖት ተከታዮች ዘንድ ይከበራል። በኢትዮጵያም በዓሉ ዛሬ ከምሽቱ ሁለት ሰዓት ጀምሮ በሚካሄድ ልዩ ልዩ ሃይማኖታዊ ሥነ ሥርዓት ሲከበር ቆይቶ፣ ከሌሊቱ ስድስት ሰዓት ላይ የቅዳሴው ሥርዓት ይካድና ከሌሊቱ ዘጠኝ ሰዓት ላይ ጠቅላላ በዓሉ ይጠናቀቃል።