በሊብያ አዲስ የአንድነት መንግሥት ምሥረታ

Your browser doesn’t support HTML5

ሊብያ ውስጥ የሚገኙ ሁለት ተቀናቃኝ ምክር ቤቶች አዲስ የአንድነት መንግሥት ለመመስረት ተስማሙ። ምክር ቤቶቹ ከዚህ ስምምነት የደረሱት፣ በሞሮኮዋ የመዝናኛ ከተማ ስኪራት (Skhirat) ላይ ባካሄዱትና በርካታ መሰናክሎችን በድል በተወጡበት ውይይት ሲሆን፣ አዲስ ጠቅላይ ሚኒስትር የሰየሙም መሆናቸው ታውቋል።