ኢትዮጵያውያን ፍልሰተኞች ከማላዊ ሊመለሱ ነው ተባለ

Your browser doesn’t support HTML5

በተለያዩ የማላዊ እስር ቤቶች የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ፍልሰተኞች በቅርቡ ወዳገራቸው እንደሚጓጓዙ፣ IOM-ዓለማቀፉ የፍልሰተኞች ድርጅትና ማላዊ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ለቪኦኤ ገለጹ። ይህ የተገለጸው ዋና ጽ/ቤታቸው ኬንያ-ናይሮቢ የሆነውና ማላዊንም የሚያካትቱት አምባሳደር ዲና ሙፍቲ በትናንቱ ዕለት ማላዊ ተገኝተው እዚያ ለሚገኙ የIOM, የMSF-ድንበር-የለሽ የሐኪሞች ድርጅትና የኢትዮጵያ ማኅበረሰብ አባላት ባረረጋገጡበት ወቅት ነው።