የቡሩንዲ መንግስት ብሄራዊ ውይይት ለማካሄድ ዝግጁ መሆኑን አስታወቀ

Your browser doesn’t support HTML5

የቡሩንዲ መንግስት በሀገር ውስጥም ሆነ በውጭ ሀገር ከመላ የሀገሪቱ ህዝብ ጋር ለመነጋገር ዝግጁ እንደሆነ አስታውቋል። መንግስት ይህን ያለው በምስራቅ አፍሪቃ ማህበረሰብ አስተባባሪነትና በኡጋንዳው ፕረዚዳንት ዩዌሪ ሙሴቬኒ ሸምጋይነት ከሚመለከተው የሀገሪቱ ህዝብ ጋር አካታች የሆነ ውይይት እንዲካሄድ የተባበሩት መንግስታት ድርጅትና የአፍሪቃ ህብረት ባለፈው ሳምናት ጥሪ ካደረጉ በኋላ ነው።