እሥራኤል የኢትዮጵያ አይሁዶችን ለማስፈር ፈቀደች

Your browser doesn’t support HTML5

ውሳኔው፥ ቤተ እሥራኤላውያኑን በአይሁዳዊቱ ሀገር ለማስፈር ለበርካታ ዓመታት ሲያከራክር ለቆየው የመብት ጥያቄ ምላሽ ያስገኛል ተብሎ ታምኖበታል። ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ በዛሬው መግለጫቸው፥ በአዲስ አበባና ጎንደር የሽግግር ካምፖች የቆዩትን የኢትዮጵያ አይሁዶች ወደ እሥራኤል ለማምጣት ጠቃሚ እርምጃ ወስደናል ብለዋል።