አሜሪካ የአልሸባብን መሪዎች የሚያስይዝ መረጃ ለሚጠቁም ወሮታ መደበች

Your browser doesn’t support HTML5

የዩናይትድ ስቴትስ መንግሥት ዋናው የአል-ሸባብ መሪ አቡ ኡቤይዳ ያለበትን የሚጠቁም መረጃ ለሚሰጥ እስከ ስድስት ሚሊዮን ዶላር የሚደርስ ወሮታ እንደሚሸልም አውጇል። አቡ ኡቤይዳ የረጅም ጊዜው የቡድኑ መሪ አህመድ አብዲ ጎዳኔ ባለፈው ዓመት መስከረም ወር በዩናይትድ ስቴትስ ኣብራሪ አልባ ኣውሮፕላን ድሮን ከተገደለ በሁዋላ መሪነቱን የተረከበው ነው።