የዲሞክራሲያዊት ኮንጎ መንግስት ምርጫዎችን የሚያመቻች “ተጨባጭ ርምጃ" እንዲወስድ ዩናይትድ ስቴትስ አሳሰበች

  • ቆንጂት ታየ

Your browser doesn’t support HTML5

የዲሞክራሲያዊት ኮንጎ ሪፑብሊክ መንግስት በሀገሪቱ ወደፊት ለሚካሄዱ ምርጫዎች ለመዘጋጀት ተጨባጭ ርምጃዎች እንዲወስድ በሀገሪቱ ጉብኝት ላይ ያሉ ኣንድ ከፍተኛ የዩናይትድ ስቴትስ ዲፕሎማት ኣሳሰቡ። በተጨማሪም የሀገሪቱን ግጭቶች ለመፍታት የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ተልእኮ በሚያደርገው ጥረት መንግስት ሙሉ በሙሉ እንዲተባበር ተማጽነዋል።