ከወይዘሮ ምስራቅ ገሰሰ ጋር ስለጡት ካንሰር የተደረገ ቃለ ምልልስ

  • ቆንጂት ታየ

የጡት ካንሰር

እ.ኤ.አ. ይህ ጥቅምት ወይም ኦክቶበር ወር የጡት ካንሰር ግንዛቤ ማስጨበጫ ወር ነው ። ስለበሽታው ምርመራ ፥ እና ህክምና ፥ማን በበሽታው ይበልጥ ተጋላጭ ነው? በምን ምክንያት ፥ የህክምናና ምርመራው ደረጃስ ከጊዜ ወደጊዜ ምን ያህል እየተራቀቀ መጥቷል? ወዘተረፈ በዚህ ወር ትኩረት ይሰጠዋል ፥ ምርመራው ወሳኝ ነውና ሴቶች ይህን እንዲገነዘቡ በተለያዩ መንገዶች ቅስቀሳ ይደረጋል፡

ወይዘሮ ምስራቅ ገሰሰ


ወይዘሮ ምስራቅ ገሰሰ ይባላሉ፥ በካሊፎርኒያ አፕል ቫሊ ነዋሪ የጤና ጥበቃ አስተዳደር ኃላፊ ናቸው ትምህርታቸውም የህዝብ ጤና ጥበቃ ነው።

እህቶቼን ኢትዮጲያውያት ይህ የጡት ካንሰር ቶሎ ከተደረሰበትና ከታከሙት መዳን እንደሚቻል እኔ በራሴ ተመክሮ የማውቀው ነውና እንዳይፈሩ ከመመርመርና መታከም እንዳይዘናጉ መምከር እፈልጋለሁ ብለው የተነሱ ናቸው ። ለሌሎችም እርስ በርስ በመማማር ህይወትን ማትረፍ ያስፈልገናል በማለት ጥሪ ያሰማሉ።

Your browser doesn’t support HTML5

ወሩን ምክንያት በማድረግ ወይዘሮ ምስራቅ ገሰሰ ጋር የተደረገውን ሰፋ ያለ ቃለ መጠይቅ ያድምጡ