በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

ረሃብ በአፍሪካ

Sorry! No content for 5 ፌብሩወሪ. See content from before

ረቡዕ 31 ጃንዩወሪ 2024

በትግራይ “ከባድ ረኀብ አንዣቧል” ያሉት ጌታቸው ረዳ የዳያስፖራውን ድጋፍ ተማፀኑ
please wait

No media source currently available

0:00 0:04:58 0:00

የትግራይ ክልልን የሰላም ግንባታ እና መልሶ ማቋቋም አዳጋች የሚያደርግ፣ ከባድ የረኀብ አደጋ እያንዣበበ እንደሆነ ያመለከቱት የጊዜያዊ አስተዳደሩ ፕሬዚዳንት ጌታቸው ረዳ፣ ለትግራይ ዳያስፖራ ማኅበረሰብ የድጋፍ ጥሪ አቅርበዋል።

“የሰላም ግንባታ እና ፍትሕ በድኅረ ጦርነት ትግራይ” በሚል ርእስ፣ ባለፈው ሳምንት ቅዳሜ፣ በድረ ገጽ በተካሔደው ዓለም አቀፍ ኮንፈረንስ ላይ አቶ ጌታቸው ሲናገሩ፣ ሕዝቡን ከረኀብ አደጋ ለመታደግና በጦርነቱ የወደመውን መንግሥታዊ መዋቅር ወደነበረበት ለመመለስ የዳያስፖራ ማኅበረሰቡ ሚና አስፈላጊ እንደሆነ ገልጸዋል፡፡

ሌላው የኮንፈረንሱ ተናጋሪ የአሜሪካ የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ ማይክ ሐመር፣ ከባድ የረኀብ አደጋ እንደሚኖር በአቶ ጌታቸው የተገለጸውን ከፍተኛ ስጋት እንደሚጋሩ ጠቅሰው፣ ከብዙ አጋሮቻችንና ለጋሾች ጋራ በትብብር መሥራታችን እንቀጥላለን፤ ብለዋል። በስርቆት ምክንያት ተቋርጦ የነበረው የምግብ ርዳታ ማከፋፈል፣ አሁን በአጥጋቢ ሁኔታ መግባባት ስለተደረሰበት ምግብ ማከፋፈሉ ተጀምሯል፤ ሲሉም አክለዋል፡፡

“ለሰላም፣ ፍትሕ እና ተጠያቂነት አስፈላጊ ሐሳቦችን ለማሰባሰብ” ታልሞ እንደተዘጋጀ በተገለጸው በዚኹ ዓለም አቀፍ የድረ ገጽ ኮንፈረንስ፣ በፕሪቶርያው የሰላም ስምምነት አፈጻጸም እስከ አሁን የታየው ፍጥነት “አላረካንም” ሲሉ መጓተቱን ማይክ ሐመር አመልክተዋል፡፡ “የኤርትራ ኀይሎች ሙሉ በሙሉ ከትግራይ

ክልል የሚወጡበትን ቀን እየጠበቅን ነው፤” ያሉት ልዩ መልዕክተኛው፣ ለተጠያቂነት መረጋገጥም “ቁርጠኞች ነን” ብለዋል፡፡

በኦሮሚያ ክልል ያለውን ግጭት ለመፍታት ጥረታቸውን እንደሚቀጥሉ ገልጸው፣ በአማራ ክልልም በፌደራል መንግሥቱ እና በፋኖ ታጣቂዎች መካከል ድርድር እንዲካሔድ ለመገፋፋት “ፍላጎታችን ነው፤” ብለዋል። ኢትዮጵያ እና ሶማሊላንድ ከተፈራረሙት የመግባቢያ ሰነድ ጋራ በተያያዘ፣ ከሶማሊያ ጋራ የተፈጠረውን መካረር ያነሡት ሐመር፣ ሁሉም የአፍሪካ ቀንድ ሀገራት ቀጣናው ሊሸከመው የማይችለውን ሌላ ግጭት እንዲያስወግዱ ጥሪ አቅርበዋል።

የሰላም ስምምነቱ ከተፈረመ 14 ወራት እንደተቆጠሩ ያወሱት ጌታቸው ረዳ ደግሞ፣ የተፈናቀለው ሕዝብ ወደ ቀዬው ሳይመለስና ሕገ መንግሥታዊ የትግራይ ክልል ግዛታዊ አንድነት ሳይረጋገጥ፣ ሰላሙ መሠረት ሊኖረው እንደማይችል አሳስበዋል፡፡ ፕሬዚዳንቱ አያይዘው እንዳመለከቱት፣ ሰላሙ የተሟላ ሊሆን የሚችለው ደግሞ፣ በፌደራል መንግሥቱ በተገለጸው የሽግግር ፍትሕ ሒደት፣ ዓለም አቀፍ የፍትሕ አካላት የተካተቱበትና የትግራይ ክልል የተሳተፈበት ተጠያቂነት ሲረጋገጥ ነው፡፡

ዘገባውን ያጠናቀረው የትግርኛ ክፍል ባልደረባ ገብረ ገብረ መድኅን ነው፤ ሀብታሙ ሥዩም በድምጽ አቅርቦታል።

የኢትዮጵያ ካርታ
የኢትዮጵያ ካርታ
“የሰሜን ጎንደር ነዋሪዎች በድርቁ ምክንያት ወደ ከተሞች እየተሰደዱ ነው”- ዩኤንኦቻ
please wait

No media source currently available

0:00 0:06:37 0:00

በአማራ ክልል፣ ሰሜን ጎንደር ዞን፣ ጃናሞራና ጠለምት ወረዳዎች በተከሰተው ድርቅ ምክንያት ከአራት ሺ በላይ ሰዎች ከመኖሪያ ከቀያቸውን ለቀው ወደ ከተሞች መሰደዳቸውን የተባበሩት መንግሥታት የሰብዓዊ ጉዳዮች ማስተባበሪያ ቢሮ (UN-OCHA) ትናንት ባወጣው ሪፖርት አስታውቋል።

በሁለቱ ወረዳዎች በተከሰተው ድርቅ ከ86 ሺ በላይ የቤት እንስሳት መሞታቸውን እና ከ173 ሺህ በላይ መሰደዳቸውን ሪፖርቱ አመልክቷል።

የጃን አሞራ ወረዳ ግብርና ፅ/ ቤት በበኩሉ፣ በሶስት ወራት ውስጥ ብቻ 1ሺ 4 መቶ ሰዎች ቤታቸውን ለቀው ወደ ከተሞች መሰደዳቸውን ዛሬ ለአሜሪካ ድምፅ አረጋግጠዋል።

ድርቁ ባስከተለው ረኀብ ምክንያት ጠለምት ወረዳን ለቀው አራት ቀን በእግር ተጉዘው በአጎራባቹ አድርቃይ ከተማ እንደሚገኙ የአሜሪካ ድምጽ ያነጋገራቸው ነዋሪዎች ገልጸዋል።

የተባበሩት መንግሥታት የሰብዓዊ ጉዳዮች ማስተባበርያ ቢሮ(UN-OCHA)፣ ከአንድ ወር በፊት ባወጣው ሪፖርቱ፣ በአማራ ክልል፣ 2 ነጥብ 8 ሚሊዮን ሕዝብ የምግብ ዋስትና ችግር እንዳለበት ጠቅሶ፣ የመንግሥት ምላሽ ያገኙት 25 በመቶ ያህሉ ብቻ እንደሆኑና በስምንት ዞኖች ውስጥ የሚገኙ 713 ሺህ ሰዎች ለአደጋ እንደተጋለጡ ማመልከቱ የሚታወስ ነው፡፡

በዐማራ ክልል፣ ሰሜን ጎንደር ዞን፣ ሦስት ወረዳዎች፣ ማለትም በጃን አሞራ፣ በየዳ እና ጠለምት ወረዳዎች፣ በ2015/16 መኸር ምርት የተከሠተው ድርቅ ባስከተለው ረኀብ፣ 36 ሰዎች መሞታቸውን እና ከ72 ሺ በላይ እንስሳትም መሞታቸውን በአካባቢው የሚገኘው የደባርቅ ዩኒቨርስቲ “ከአንድ ወር በፊት አደረግኩት” ባለው ጥናት ይፋ አድርጎ ነበር።

የተባበሩት መንግሥታት የሰብዓዊ ጉዳዮች ማስተባበሪያ ቢሮ (UN-OCHA) ትናንት ባወጣው ሪፖርቱ ከድርቁ ጋር በተያያዘ በአማራ ክልል፣ ጠለምትና ጃን አሞራን ጨምሮ 2 ነጥብ 5 ሚሊዮን ህፃናት ትምህርት ማቋረጣቸውንም ገልፆል።

የፌደራል አደጋ ሥጋት አመራር ኮሚሽን እና በኢትዮጵያ የተባበሩት መንግሥታት የሰብዓዊ እርዳታ አስተባባሪ በሀገሪቱ ያለውን ወቅታዊ የሰብዓዊ እርዳታ አቅርቦት በተመለከተ በጋራ ባወጡት መግለጫ በኢትዮጵያ በአምስት ክልሎች 4 ሚሊዮን የሚጠጉ ዜጎች አስቸኳይ የምግብ ድጋፍ እንደሚያስፈልጋቸው መግለጻቸው ይታወሳል፡፡

ተጨማሪ ይጫኑ

XS
SM
MD
LG