በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

ረሃብ በአፍሪካ

Sorry! No content for 28 ጃንዩወሪ. See content from before

ዓርብ 12 ጃንዩወሪ 2024

የኢትዮጵያ ካርታ
የኢትዮጵያ ካርታ
“የሰሜን ጎንደር ነዋሪዎች በድርቁ ምክንያት ወደ ከተሞች እየተሰደዱ ነው”- ዩኤንኦቻ
please wait

No media source currently available

0:00 0:06:37 0:00

በአማራ ክልል፣ ሰሜን ጎንደር ዞን፣ ጃናሞራና ጠለምት ወረዳዎች በተከሰተው ድርቅ ምክንያት ከአራት ሺ በላይ ሰዎች ከመኖሪያ ከቀያቸውን ለቀው ወደ ከተሞች መሰደዳቸውን የተባበሩት መንግሥታት የሰብዓዊ ጉዳዮች ማስተባበሪያ ቢሮ (UN-OCHA) ትናንት ባወጣው ሪፖርት አስታውቋል።

በሁለቱ ወረዳዎች በተከሰተው ድርቅ ከ86 ሺ በላይ የቤት እንስሳት መሞታቸውን እና ከ173 ሺህ በላይ መሰደዳቸውን ሪፖርቱ አመልክቷል።

የጃን አሞራ ወረዳ ግብርና ፅ/ ቤት በበኩሉ፣ በሶስት ወራት ውስጥ ብቻ 1ሺ 4 መቶ ሰዎች ቤታቸውን ለቀው ወደ ከተሞች መሰደዳቸውን ዛሬ ለአሜሪካ ድምፅ አረጋግጠዋል።

ድርቁ ባስከተለው ረኀብ ምክንያት ጠለምት ወረዳን ለቀው አራት ቀን በእግር ተጉዘው በአጎራባቹ አድርቃይ ከተማ እንደሚገኙ የአሜሪካ ድምጽ ያነጋገራቸው ነዋሪዎች ገልጸዋል።

የተባበሩት መንግሥታት የሰብዓዊ ጉዳዮች ማስተባበርያ ቢሮ(UN-OCHA)፣ ከአንድ ወር በፊት ባወጣው ሪፖርቱ፣ በአማራ ክልል፣ 2 ነጥብ 8 ሚሊዮን ሕዝብ የምግብ ዋስትና ችግር እንዳለበት ጠቅሶ፣ የመንግሥት ምላሽ ያገኙት 25 በመቶ ያህሉ ብቻ እንደሆኑና በስምንት ዞኖች ውስጥ የሚገኙ 713 ሺህ ሰዎች ለአደጋ እንደተጋለጡ ማመልከቱ የሚታወስ ነው፡፡

በዐማራ ክልል፣ ሰሜን ጎንደር ዞን፣ ሦስት ወረዳዎች፣ ማለትም በጃን አሞራ፣ በየዳ እና ጠለምት ወረዳዎች፣ በ2015/16 መኸር ምርት የተከሠተው ድርቅ ባስከተለው ረኀብ፣ 36 ሰዎች መሞታቸውን እና ከ72 ሺ በላይ እንስሳትም መሞታቸውን በአካባቢው የሚገኘው የደባርቅ ዩኒቨርስቲ “ከአንድ ወር በፊት አደረግኩት” ባለው ጥናት ይፋ አድርጎ ነበር።

የተባበሩት መንግሥታት የሰብዓዊ ጉዳዮች ማስተባበሪያ ቢሮ (UN-OCHA) ትናንት ባወጣው ሪፖርቱ ከድርቁ ጋር በተያያዘ በአማራ ክልል፣ ጠለምትና ጃን አሞራን ጨምሮ 2 ነጥብ 5 ሚሊዮን ህፃናት ትምህርት ማቋረጣቸውንም ገልፆል።

የፌደራል አደጋ ሥጋት አመራር ኮሚሽን እና በኢትዮጵያ የተባበሩት መንግሥታት የሰብዓዊ እርዳታ አስተባባሪ በሀገሪቱ ያለውን ወቅታዊ የሰብዓዊ እርዳታ አቅርቦት በተመለከተ በጋራ ባወጡት መግለጫ በኢትዮጵያ በአምስት ክልሎች 4 ሚሊዮን የሚጠጉ ዜጎች አስቸኳይ የምግብ ድጋፍ እንደሚያስፈልጋቸው መግለጻቸው ይታወሳል፡፡

ፎቶ ፋይል፦ግጭቱን ሸሽተው አድሬ በሚገኘው ኦውራንግ የስደተኞች መጠለያ ጣቢያ የሚገኙ ሱዳናውያን ውሃ ለመቅዳት ወረፋ ያዘው እአአ ታኅሣስ 7/2023
ፎቶ ፋይል፦ግጭቱን ሸሽተው አድሬ በሚገኘው ኦውራንግ የስደተኞች መጠለያ ጣቢያ የሚገኙ ሱዳናውያን ውሃ ለመቅዳት ወረፋ ያዘው እአአ ታኅሣስ 7/2023

በሱዳን በመካሄድ ላይ ያለው የሁለት ጀኔራሎች ጦርነት ከካርቱም በስተ ደቡብ ወደምትገኘውና አል-ጃዚራ ወደተሰኘችው ለም አካባቢ ከተዛመተ ወዲህ፣ በአንድ ወቅት ትርፍ ያመርቱ የነበሩ ገበሬዎች ምጽዋት ጠባቂ ሆነዋል።

ገበሬዎቹ ወደ ማሳቸው መሄድ እንዳልቻሉ እና የዘሩትን መንከባከብም ሆነ መሰብሰብ እንዳልቻሉ ለኤ.ኤፍ.ፒ ዜና ወኪል ተናግረዋል።

በሱዳን መደበኛ ሰራዊት እና በፈጥኖ ደራሽ ኃይሉ መካከል ባለፈው ሚያዚያ ጦርነቱ ከጀመረ ወዲህ፣ አል-ጃዚራ ከግማሽ ሚሊዮን በላይ ለሚሆኑ ሰዎች መጠለያ እንደሆነበረች የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት አስታውቋል።

ጦርነቱ ወደ ደቡብ አቅጣጫ እየተስፋፋ በመምጣቱ ግን፣ ባሳለፍነው ታህሳስ ወር በአል-ጃዚራ የነበረው ሰላም ደፍርሷል። ዋድ ማዳኒ የተሰኘችውን ከተማ ለመቆጣጠር ውጊያው በመፋፋሙ፣ በመቶ ሺሕ የሚቆጠሩ ሰዎች ለመሸሽ ተገደዋል።

የሱዳን ሠራዊት ዋድ ማዳኒን ጥሎ ሲወጣ፣ የፈጥኖ ደራሽ ኃይሉ ሰፊ የእርሻ መሬቶችን በመቆጣጠሩ፣ ሰዎች መንደራቸውን ለቆ ለመውጣትም ሆነ በመስኖ እና ማዳበሪያ የሚለሙ ሰፋፊ እርሻዎቻቸውን ለመንከባከብ እንዳይቹሉ አድርጓል።

የተመድ የዓለም የምግብ ፕሮግራም እንደሚለው፣ በአሁኑ ወቅት 18 ሚሊዮን የሚሆኑ ሰዎች ከረሃብ ጋር ተፋጠዋል። አምስት ሚሊዮን የሚሆኑቱ ደግሞ አስቸኳይ መልስ የሚያሻው ሁኔታ ውስጥ ናቸው።

ረሃብ በይፋ ባይታወጅም፣ መከሰቱ አይቀሬ መሆኑን ‘የኖርዌ ፍልሰተኞች ም/ቤት’ የተሰኘው ግብረ ሰናይ ድርጅት ሲያስታውቅ፣ የአሜሪካው ዓለም አቀፍ የልማት ድርጅት (ዩኤስኤይድ) በበኩሉ፣ ጦርነቱ ሰብል አምራች በሆኑ አካባቢዎች መስፋፋቱ፣ የአገሪቱን የምግብ ዋስትና አደጋ ላይ እንደጣለ አመልክቷል።

በሱዳን ዘጠኝ ወራት ያስቆጠርውን ጦርነት ለማስቆም እና የሰብዓዊ ሥራ ለማከናወን እንዲቻል፣ ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ “አስቸኳይ እና ወሳኝ” እርምጃ መውሰድ እንዳለበት የተመድ የአስቸኳይ ግዜ አስተባባሪ ማርቲን ግሪፊትስ ባለፈው ሐሙስ አሳስበዋል።

በዚህ ዓመት ሃያ አምስት ሚሊዮን የሚሆኑ ሱዳናውያን ርዳታ እንደሚያሻቸው የጠቀሱት ኃላፊው፣ ውጊያው የሚቀጥል ከሆነ ግን ርዳታ የማድረስ ሥራው እንደሚስተጓጎል ሥጋታቸውን ገልጸዋል።

ተጨማሪ ይጫኑ

XS
SM
MD
LG