በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

የሱዳን ስደተኞች በኢትዮጵያ


ሱዳንና ደቡብ ሱዳን ድንበር ላይ በቅርቡ የተቀሰቀሰው ውጊያ ከሔግሊጅ፥ ከታሎዲና ከሌሎች በደቡብ ሱዳን ኮርዶፋን ክፍለ ሀገር የሚገኙ ከተሞች 35 ሺህ የሚጠጉ ሰዎችን አፈናቅሏል።

በተባበሩት መንግሥታት የስደተኞች ጉዳይ ከፍተኛ ኮሚሽነር /ዩኤንኤችሲአር/ መግለጫ መሠረት ድርጅቱ በያዝነው ሚያዝያ ወር ውስጥ ብቻ ከብሉ ናይል ስቴት አዲስ የተፈናቀሉ 2 ሺህ 400 ስደተኞችን በጎረቤት ኢትዮጵያ በቤንሻንጉል ጉምዝ ካምፖች ተቀብሏል።

ይህንኑ ትናንት ሐሙስ የወጣውን የመንግሥታቱን ድርጅት የስደተኞች ጉዳይ ከፍተኛ ኮሚሽነር መግለጫ መነሻ በማድረግ የኮሚሽነሩ የአዲስ አበባ ፅ/ቤት ቃል አቀባይ አቶ ክሱት ገብረእግዚአብሔር ለቪኦኤ መግለጫ ሰጥተዋል፡፡

ዝርዝሩን ያዳምጡ፡፡

XS
SM
MD
LG