በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

በገላና ወረዳ የጸጥታ ችግር ወደ ሐዋሳ የሚያደርሰው መንገድ መዘጋቱ ተገለጸ


በገላና ወረዳ የጸጥታ ችግር ወደ ሐዋሳ የሚያደርሰው መንገድ መዘጋቱ ተገለጸ
please wait

No media source currently available

0:00 0:05:19 0:00

በገላና ወረዳ የጸጥታ ችግር ወደ ሐዋሳ የሚያደርሰው መንገድ መዘጋቱ ተገለጸ

በምዕራብ ጉጂ ዞን የገላና ወረዳ አንዳንድ ቀበሌዎች፣ “ኦነግ ሸኔ” ሲሉ በጠሩት ታጣቂ ቁጥጥር ሥር እንደዋሉ የገለጹ የአካባቢዎቹ ነዋሪዎች እና ባለሥልጣናት፣ ከአማሮ ኬሌ- ቶሬ - ይርጋጨፌ - ዲላ ወደ ሐዋሳ የሚያደርሰው መንገድ መዘጋቱን እና የሰላማዊ ዜጎች እንቅስቅሴ መገደቡን ተናግረዋል።

የኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ጉጂ ዞን ገላና ወረዳ የጸጥታ እና አስተዳደር ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ኢያሱ ጂኦ፣ በጉዳዩ ላይ ምላሽ ለመስጠት ቃል ቢገቡም ስብሰባ ውስጥ መሆናቸውን የሚገልጽ አጭር የጽሑፍ መልዕክት ከመላክ በቀር ማብራሪያ አልሰጡንም፡፡

የምዕራብ ጎጂ ዞንን በሚያጎራብተው የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ኮሬ ዞን የኬሌ ከተማ ፖሊስ አዛዥ ኮማንደር አበበ ጣሰው፣ ላለፉት አራት ቀናት መንገዱ የተዘጋበት ምክንያት፣ እርሳቸው ኦነግ ሸኔ ያሉት የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት አካባቢውን በመውረሩ እንደኾነ መስማታቸውን ተናግረዋል።

የኦሮሞ ነፃነት ሠራዊት ዓለም አቀፍ ቃለ አቀባይ እና በዩናይትድ ስቴትስ ቨርጂኒያ የሚኖሩት ኦዳ ተርቢ፤ ቡድናቸው ለተከሰሰበት ጉዳይ ምላሽ እንዲሰጡ ያደረግነው ሙከራ አልተሳካም።

ዝርዝር ዘገባውን ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።

መድረክ / ፎረም

XS
SM
MD
LG