በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

በሰሜን ተራሮች ብሔራዊ ፓርክ የተነሣን የእሳት ቃጠሎ ለማስቆም ጥረቱ ቀጥሏል


በሰሜን ተራሮች ብሔራዊ ፓርክ የተነሣን የእሳት ቃጠሎ ለማስቆም ጥረቱ ቀጥሏል
please wait

No media source currently available

0:00 0:02:49 0:00

በሰሜን ጎንደር ዞን በሚገኘው የሰሜን ተራሮች ብሔራዊ ፓርክ ውስጥ የተነሣውን የእሳት ቃጠሎ ለማስቆም ጥረት እየተደረገ መኾኑን፣ የዞኑ አስተዳደር አስታወቀ፡፡

የሰሜን ጎንደር ዞን ምክትል አስተዳዳሪ አቶ ቢምረው ካሳ፣ ዛሬ ሰኞ ከአሜሪካ ድምፅ ጋራ ባደረጉት ቆይታ፣ ካለፈው ሳምንት ኀሙስ ጀምሮ እስከ ዛሬ ድረስ በፓርኩ ውስጥ የተነሣውን ቃጠሎ ለመቆጣጠር፣ የአካባቢው ነዋሪዎች ርብርብ እያደረጉ መኾኑንና ከአጎራባች ቀበሌዎች ተጨማሪ ሰዎች ወደ ስፍራው መላካቸውን ገልጸዋል፡፡

እስከ አሁን በቃጠሎው የደረሰው ጉዳት በውል አልታወቀም፤ ያሉት አቶ ቢምረው፣ ከዞንና ከወረዳ የተውጣጣ ቡድን እንዲያጠና መላኩን አመልክተዋል፡፡

ዝርዝር ዘገባውን ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።

XS
SM
MD
LG