በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

በልዩ ዞኑ ባቲ ወረዳ በተከሠተው የኮሌራ ወረርሽኝ ሁለት ሰዎች መሞታቸው ተገለጸ


በልዩ ዞኑ ባቲ ወረዳ በተከሠተው የኮሌራ ወረርሽኝ ሁለት ሰዎች መሞታቸው ተገለጸ
please wait

No media source currently available

0:00 0:02:40 0:00

በአማራ ክልል በኦሮሞ ብሔረሰብ አስተዳደር ዞን ባቲ ወረዳ በሦስት ቀበሌዎች በያዝነው ሚያዝያ ወር በተከሠተው የኮሌራ ወረርሽኝ ሁለት ሰዎች መሞታቸውን፣ የአማራ ክልል የኅብረተሰብ ጤና ኢንስትቲዩት አስታወቀ፡፡

የኢንስትቲዩቱ ዋና ዲሬክተር አቶ በላይ በዛብህ ለአሜሪካ ድምፅ እንደተናገሩት፣ በወረዳው በሦስት ቀበሌዎች በተዛመተው የኮሌራ ወረርሽኝ 162 ሰዎች ሲያዙ፣ ከእነዚህም ውስጥ ሁለቱ ሕይወታቸው አልፏል፡፡

ቀሪዎቹ ወደ ሕክምና ተቋማት ተወስደው በቂ ክትትል እና ድጋፍ እየተደረገላቸው እንደኾነ የገለጹት አቶ በላይ፣ ወረርሽኙ እንዳይስፋፋ ከክልል እስከ ወረዳ ባሉ ባለሞያዎች በትኩረት እየተሠራ ነው፤ ብለዋል፡፡

ሙሉ ዘገባውን ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።

XS
SM
MD
LG