ቅዳሜ, ሜይ 25, 2013 የአካባቢው ጊዜ 03:15

የአፍሪካ ቀንድ

የኦርኬስትራ ኢትዮጵያው መሪ፥ አንጋፋው የሙዚቃ ሠው ተስፋዬ ለማ አረፈ።

«ከአርባ ስድስት ዓመታት በፊት የአሜሪካ የሰላም ጓድ ሆኜ ወደ ኢትዮጵያ በተጓዝኩበት ጊዜ በኢትዮጵያ የባህል ሙዚቃ ስማረክ የተዋወቅኩት ተሥፋዬ ለማ ለኢትዮጵያ የባህል ሙዚቃ ከፍተኛ አስተዋጽ ያደረገ ሰው ነው።» ቻርልስ ሳተን።

Tesfaye LemmaTesfaye Lemma
x
Tesfaye Lemma
Tesfaye Lemma
የፊደል ቁመት - +
አሉላ ከበደ


በአንዳንዶች የኢትዮጵያ የባህል ሙዚቃ አባት የሚል የቁልምጫ ሥም የተሰጠው እውቁ ሙዚቃ ሰው ተሥፋዬ ለማ ባለፈው ሃሙስ ለሊት፥ ለአርብ አጥቢያ ከዚህ ዓለም በሞት ተለይቷል።

ተሥፋዬ ለማ «ኦርኬስትራ ኢትዮጵያ፤» በሚል ይታወቅ የነበረው የቀድሞውን የቀዳማዊ ኃይለሥላሴ፥ የዛሬውን አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የባህል ሙዚቃ ባንድ በመራባቸው ዓመታት፥ የኢትዮጵያ የባህል ሙዚቃ በአጠቃላይ የኅብረተሰቡንም ሆነ የሌሎች ተቀባይነትና ተሰሚነት ማስገኘት ባስቻሉ ሥራዎቹ ይወደሳል።

ተሥፋዬ ለማ ከኦርኬስትራ ኢትዮጵያ በኋላም በተለያዩ የሙዚቃ ተቋማት ባከናወናቸው ሥራዎቹ፥ ባፈራቸው ታዋቂ ድምጻውያን እና እንዲሁም ጥላሁን ገሰሰን ጨምሮ ለገናና ድምጻውያን በጻፋቸው የሙዚቃ ድርሰቶቹም ይታወቃል።

ተስፋዬ፥ የህክምና ክትትልና እገዛ ከሚያገኝበት የአዛውንቶች መኖሪያ ሳለ የደረሰውን በኢትዮጵያ የባህል ሙዚቃ ታሪክ ላይ ያተኮረ ዳጎስ ያሉ ገጾች ያሉት መጽሃፍ ለማሳተም ጥረት በማድረግ ላይ ሳለ ነው፥ ከዚህ ዓለም በሞት የተለየው።  

የአንጋፋውን የሙዚቃ ሠው ተሥፋዬ ለማን ህይወትና ሥራ ለመዘከር የተሰናዱትን ቅንብሮች ከዚህ ያድምጡ።

ቆይታ ከሁለገቧ አርቲስት ዓለም ጸሃይ ወዳጆና ከአርቲስት ዓለማየሁ ገብረህይወት ጋር
Loading
12:00:00 / -:--:--

ቆይታ ከተሥፋዬ ለማ የእድሜ ልክ ወዳጅ፥ Charles Sutton ጋር
Loading
12:00:00 / -:--:--
ይህ ፎረም ተዘግቷል
አስተያየቶች
     
እዚህ ፎረም ላይ የሠፈረ አስተያየት የለም፤ ያውጡና የመጀመሪያው ይሁኑ