በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

ፍቼ - ጨምበላላ፣ እሥራቶች፣ ሲአንና የዞኑ አስተዳደር


ሲዳማ ዞን (በደማቅ የተከበበው)
ሲዳማ ዞን (በደማቅ የተከበበው)

አባሎቹና ደጋፊዎቹ እንዲሁም ሌሎችም የሕብረተሰብ ክፍሎች በተለያዩ የሲዳማ ዞን ወረዳዎች ውስጥ እየታሠሩ እንደሚጉላሉ የሲዳማ አርነት ንቅናቄ አስታወቀ፤ የታሠሩት በሕገወጥ ተግባር ላይ በመሠማራታቸው ነው ሲል ዞኑ ይናገራል፡፡


please wait

No media source currently available

0:00 0:12:26 0:00
ቀጥተኛ መገናኛ


በሲዳማ ዞን ሃያ አንዱም ወረዳዎች ውስጥና በሃዋሣ ከተማ በርካታ አባሎቻቸው፣ ደጋፊዎቻቸውና ሌሎችም የሕብረተሰብ ክፍሎች እየታሠሩ መሆኑን የነገሩን የሲዳማ አርነት ንቅናቄ ሊቀመንበር ዶ/ር ሚሊዮን ቱማቶ ናቸው፡፡

ነሐሴ 9 ቀን 2004 ዓ.ም ከተከበረው ፍቼ ተብሎ የሚታወቀው የዘመን መለወጫ በዓልና እርሱንም ተከትሎ በዋለው ጨምበላላ ባሕላዊ ጨዋታ ወቅት እንዲሁም ከዚያም በኋላ እሥራቱ መቀጠሉን የሚናገሩት አቶ ሚሊዮን የፓርቲያቸው ሰዎችና ደጋፊዎችም ሲዳማ ክልል እንዲሆንና ሃዋሣም ቻርተርድ ሜትሮፖሊታን እንድትሆን ጠይቀው እንደነበረ አቶ ሚሊዮን ተናግረዋል፡፡

ይሁን እንጂ በፍቼ በዓል ወቅት ከድርጅታቸው ሰዎች ወገን የተነሣ አንዳችም ችግር እንዳልነበረ ገልፀዋል፡፡

የሲዳማ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሚሊዮን ማቴዎስ ለቪኦኤ በሰጡት መግለጫ በፍቼ ጨምበላላ በዓል ወቅት የታሠሩ ሰዎች እንደነበሩና ብዙዎቹ በዋስ መለቀቃቸውን አመልክተዋል፡፡

እሥራቱ የተካሄደው ፀረ-ሠላም አድራጎት ሲፈፅሙ በነበሩ ሰዎች ላይ እንደነበረ የጠቆሙት አቶ ሚሊዮን ማቴዎስ ጉዳዩ በፍርድ ቤት የተያዘ ነው በሚል ሰዎቹ የተከሰሱባቸውን ጥፋቶች ለመግለፅ አልፈቀዱም፡፡

አንድ በዞኑ ውስጥ የሚኖሩ የሲአን አባል ግን ሰዎቻቸው ሰው አክባሪና ሰላማዊም እንደነበሩ፤ በበዓሉ ወቅትም የራሣቸውን ባህል በዘፈንና በጭፈራ ከማሞገስ ያለፈ ነገር አለመፈፀማቸውን ገልፀው እንዲህ ዓይነቱ አድራጎት የድርጅታቸው ላይ ከረጅም ጊዜ ጀምሮ ሲካሄድ የቆየ ማዋከብ አካል መሆኑን ተናግረዋል፡፡

ዘገባውን ያዳምጡ፡፡
XS
SM
MD
LG